Search

Fragen und Antworten zum christlichen Glauben

Thema 1: Die Wiedergeburt aus Wasser und Geist

1-10. ኢየሱስ በመስቀል ላይ ራሱን መስዋዕት ያደረገው ለምንድነው?  

ኢየሱስ መስዋዕት የሆነው በጥምቀቱ አማካይነት ለወሰዳቸው ሐጢያቶቻችን ነበር፡፡ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ ቅጣት ነጻ መውጣት እንችል ዘንድ ለሐጢያቶቻችን ዋጋ ለመክፈል ሥጋውን ሰጠን፡፡  
እኛ ማወቅ ያለብን ኢየሱስ ሐጢያቶቻችንን ለመውሰድ በዮርዳኖስ መጠመቁን ነው፡፡ ኢየሱስ በዚህ ምክንያት በመስቀል ላይ እንደሞተ ማመን ይኖርብናል፡፡   
ኢየሱስ ከመሰቀሉ በፊት ባይጠመቅ ኖሮና በመስቀል ላይ ባይሞት ኖሮ ሐጢያቶቻችን በሙሉ ከእኛ ጋር ይቀሩ ነበር፡፡ ስለዚህ በኢየሱስ ጥምቀትና ደም ማመን አለብን፡፡ ኢየሱስ የእግዚአብሄር ልጅ የመስዋዕት በግ ስለሆነ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ለመደምሰስ መስዋዕት ሆነ፡፡   
ሁላችንም ኢየሱስ የእግዚአብሄር ልጅ እንደሆነ፣ የዓለምን ሐጢያቶች በሙሉ ለመውሰድም እንደተጠመቀና ለሐጢያቶቻችንም እንደተሰቀለ ማመን ይገባናል፡፡ እኛ ሐጢያተኞችም ከሐጢያቶቻችን ሁሉ እንዳነጻና ከቅጣት እንዳናመልጥ ተሰቀለ፡፡