Search

Mensajes en Video de los Colaboradores

እግዚአብሔር የዓለምን ኃጢአት ይቅር ያለው በአንድ ጊዜ ነው‼️ እግዚአብሔር ፍጹም ነው‼️ በአንድ ጊዜ ላንዴና ለመጨረሻ የዓለምን ኃጢአት በሙሉ ይቅር ብሏል‼️

  • Mesfin Berhanu Ubba
  • Ethiopia
  • 12/13/2021 55613

መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦
ዕብራውያን 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ሊቀ ካህናትም ሁሉ ዕለት ዕለት እያገለገለ ኃጢአትን ሊያስወግዱ ከቶ የማይችሉትን እነዚያን መሥዋዕቶች ብዙ ጊዜ እያቀረበ ቆሞአል፤
¹² እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፥

 …  
¹⁴ አንድ ጊዜ በማቅረብ የሚቀደሱትን የዘላለም ፍጹማን አድርጎአቸዋልና።
¹⁵-¹⁶ መንፈስ ቅዱስም ደግሞ ስለዚህ ይመሰክርልናል፤ ከዚያ ወራት በኋላ ከእነርሱ ጋር የምገባው ኪዳን ይህ ነው ይላል ጌታ፤ በልባቸው ሕጌን አኖራለሁ በልቡናቸውም እጽፈዋለሁ ብሎ ከተናገረ በኋላ፥
¹⁷ ኃጢአታቸውንና ዓመጻቸውንም ደግሜ አላስብም ይላል።
¹⁸ የእነዚህም ስርየት ባለበት ዘንድ፥ ከዚህ ወዲህ ስለ ኃጢአት ማቅረብ የለም።
ይላል።
_____________________________________________
እዚህ ላይ 
 "እርሱ ግን ስለ ኃጢአት #አንድን #መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ"
ሲባል
#ኢየሱስ ክርስቶስ #የዓለምን #ኃጢአት የተሸከመውና የዓለምን ኃጢአት የደመሰሰው በአንድ ጊዜ ላንዴና ለመጨረሻ ነው ማለት ነው። 
❤❤❤
እግዚአብሔር ደግሞ 
 ይህን የልጁን ሥራ ያመኑ የሰዎቹን ኃጢአታቸውንና አመጻቸውንም ደግሜ አላስብም በማለት አዲስ ኪዳን መግባቱ የሚያረጋግጥልን እግዚአብሔር የዓለምን ኃጢአት በሙሉ በአንድ ጊዜ ላንዴና ለመጨረሻ ይቅር ማለቱን ነው።...............
ሃሌሉያ‼️
____________________________________________
በተከታታይ የሚነበቡ ነጻ የክርስቲያን መጽሐፍትን በpdf, በAudio እና በመጽሐፍ ከፈለግኩ ከታች ያሉትን አድራሻዎችን በመጫን ተጠቃሚ ይሁኑ‼️
Website