Search

LIBRI STAMPATI GRATUITI,
eBOOKS E AUDIOLIBRI GRATUITI

Genesi

Amarico 54

የሰውን ዘር ከጥፋት የሚያድን የወንጌል ምስክር ሁኑ

Rev. Paul C. Jong | ISBN 9788928260454 | Pages 306

Scarica eBook e audiolibri GRATUITI

Scegli il formato file preferito e scaricalo in modo sicuro sul tuo dispositivo mobile, PC o tablet per leggere e ascoltare le raccolte di sermoni in qualsiasi momento e ovunque. Tutti gli eBook e audiolibri sono completamente gratuiti.

Puoi ascoltare l'audiolibro tramite il lettore qui sotto. 🔻
Possiedi un libro in brossura
Acquista un libro in brossura su Amazon
የማውጫ ሰሌዳ
 
መቅድም
1. የሰውን ዘር ከጥፋት ማዳን የሚችሉ የወንጌል ሰባኪዎች ሁኑ (ዘፍጥረት 6፡5-22) 
2. አሁንም እንኳን ከሐጢያቶቻችሁ መዳን አለባችሁ (ዘፍጥረት 6፡1-4) 
3. በእነዚህ የመጨረሻ ቀኖች ለደህንነታችሁ ተዘጋጁ (ዘፍጥረት 6፡5-12) 
4. በእግዚአብሄር ጽድቅ በማመን ደህንነት ላይ ደርሰናል (ዘፍጥረት 6፡5-12) 
5. እምነታችሁን በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል ላይ በማኖር ልባችሁን ጠብቁ (ዘፍጥት 6፡13-14)
6. ኢየሱስ ሐጢያቶቻችሁን በሙሉ የመደምሰሱን እውነታ ታውቃላችሁን? (ዘፍጥረት 6፡14)
7. የእግዚአብሄር ሠራተኞች (ዘፍጥረት 7፡1-24) 
8. እየቀረበ ላለው የዓለም ፍጻሜ መዘጋጀት አለባችሁ (ዘፍጥረት 7፡1-24) 
9. ወደ ደህንነት የሚወስደን እምነት (ዘፍጥረት 7፡1-13) 
10. ዓለምን በእግዚአብሄር ዓይኖች እዩት (ዘፍጥረት 7፡1-12) 
11. ወደ መርከቡ ለመግባት ያለ ማመንታት የሐጢያቶችን ስርየት መቀበል አለባችሁ (ዘፍጥረት 7፡1-5) 
12. ወደ መርከቡ ውስጥ መግባት አለባችሁ (ዘፍጥረት 7፡1-5) 
13. እግዚአብሄር ለእኛ ያለው ዕቅድና ልብ (ዘፍጥረት 8፡20-21) 
14. በእምነት ሕይወታችን ውስጥ ስምንት ወቅቶች አሉ (ዘፍጥረት 8፡22) 
 
በአንድ ወቅት በብዙዎች ትልቅ ክብር የተሰጠው አንድ መጋቢ ነበር፡፡ ይህ መጋቢ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢየሱስ የመስቀል ላይ ደም ባመነ ጊዜ ባለፉት ሐጢያቶቹ ለጎዳው ለእያንዳንዱ ሰው ካሳ በመስጠት የታወቀ ነበር፡፡ ጠለቅ ባለ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዕውቀቱና የመፈወስ ሐይሉም እንደዚሁ የታወቀ ነበር፡፡ ነገር ግን እንደ አለመታደል ሆኖ ይህ መጋቢ መጽሐፍ ቅዱስ የተናገረለትን የውሃውንና የመንፈሱን እውነተኛ ወንጌል አላወቀም፡፡ በዚህም እርሱ በእግዚአብሄር ዓይኖች ከንቱ ነው፡፡ 
ታዲያ በዛሬዎቹ ክርስቲያኖች መካከል ይህ የተምታታ እምነት ያላቸው እነማን ናቸው? እነርሱ የጌታ ደቀ መዛሙርት ከሰበኩት የውሃና የመንፈስ ወንጌል ይልቅ በመስቀሉ ደም ብቻ የሚያምኑ ሰዎች ናቸው፡፡ በእነዚህ ተቋማዊ ክርስቲያኖች የተሰበከው ወንጌል የሚናገረው ኢየሱስ በመስቀል ላይ ስላፈሰሰው ደም ነው፡፡ ይህ ሐሰተኛ ወንጌል በክርስትና ላይ ትልቅ ጉዳት በማምጣት በርካታ ምዕመናኖችን የሥነ ምግባርና የራስ ጽድቅ ተገዥዎች በማድረግና ግብዛዊ የሐይማኖት ተለማማጆች ወደ መሆን ዝቅ አድርጎ ለውጦዋቸዋል፡፡ 
ዛሬም እንኳን ከእነዚህ ክርስቲያኖች ተብዬዎች ብዙዎች አሉ፡፡ ስለዚህ የዛሬው ክርስትና በትልቅ ግራ መጋባት ተጋርዶዋል፡፡ ጌታ በዚህ ዘመንና ጊዜ እንድንይዘው የሚፈልገው ቃል ይህንን የውሃና የመንፈስ ወንጌል ነው፡፡ እውነተኛውን እምነት የሚይዙት ይህንን የውሃና የመንፈስ ወንጌል የሚያምኑና የሚሰብኩ ብቻ ናቸው፡፡ ለዚህ ምክንያቱ እነዚህ ክርስቲያኖች ሐጢያት አልባ መሆናቸው ብቻ ሳይሆን የሌሎችን ሰዎች ሐጢያቶች የመደምሰስንም ሥራ መሥራት የሚችሉ መሆናቸው ነው፡፡
Di Più
Libro Stampato Gratuito
Aggiungi questo libro al carrello
The New Life Mission

Partecipa al nostro sondaggio

Come hai saputo di noi?