Search

คำถามที่พบบ่อยเกี่ยวกับความเชื่อของคริสเตียน

เรื่องที่ 1 : การเกิดใหม่โดยน้ำและพระวิญญาณ

1-11. ኢየሱስን ያጠመቀው አጥማቂው ዮሐንስ ማነው? 

እግዚአብሄር ለእስራኤል በሙሴ አማካይነት ሕጉንና የመስዋዕት ስርዓቱን የሰጣቸው ለሐጢያቶቻቸውና ለበደሎቻቸው ስርየትን ያገኙ ዘንድ ነው፡፡ እርሱ የሙሴ ታላቅ ወንድም የነበረውን አሮንን ሊቀ ካህን አድርጎ በመሾም የእስራኤሎች ዓመታዊ ሐጢያቶች በሙሉ ይነጹ ዘንድ የስርየት ቀን በሆነው በሰባተኛው ወር በአስረኛው ቀን የስርየትን መስዋዕት እንዲያቀርብ አደረገው፡፡ (ዘሌዋውያን 16)  
እግዚአብሄር በስርየት ቀን የሚቀርበው መስዋዕት በአሮንና በእርሱ ዘሮች መካከል ባሉ የእርሱ ምትክ ሊቀ ካህናት ብቻ እንዲቀርቡ ግልጽ አድርጎዋል፡፡ እግዚአብሄር እስራኤሎች አሮን በሚለቀቀው ፍየል ራስ ላይ በሚጭናቸው እጆቹ አማካይነት ሐጢያቶቻቸውን በሙሉ እንዲያስተሰርዩ መንገድን ከፈተላቸው፡፡ እግዚአብሄር የመሰረተላቸው የስርየት ሕግ ነው፡፡   
በዚህ ጥላ ኢየሱስ የሰው አዳኝ እንደነበር በግልጽ እንዲታወቅ አደረገ፡፡ እግዚአብሄር በአዲስ ኪዳን ዘመን የአሮን ዘር፤ (1ኛ ዜና 24፡10፤ሉቃስ 1፡5) የብሉይ ኪዳን የመጨረሻው ሊቀ ካህን (ማቴዎስ 11፡1-13) የሆነውን አጥማቂውን ዮሐንስን ላከው፡፡ አጥማቂው ዮሐንስ እግዚአብሄር የላከው ነቢይ፣ የሰው ዘር ወኪልና ሊቀ ካህን በመሆኑ ሐጢያተኞችን ለማዳን በመጣው በእግዚአብሄር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ የሰውን ዘር ሐጢያቶች በሙሉ ለማስተላለፍ ኢየሱስን አጠመቀው፡፡   
ሰዎች ሁሉ በአጥማቂው ዮሐንስ አማካይነት ሐጢያቶቻቸውን ወደ ኢየሱስ ማስተላለፍ በመቻላቸው በእርግጥም ተባርከዋል፡፡ የዮሐንስ ሚና የሰውን ዘር የወከለ ሊቀ ካህንና ሐጢያቶችን ሁሉ ወደ ኢየሱስ ያስተላለፈ የእግዚአብሄር አገልጋይ መሆን ነበር፡፡   
አጥማቂው ዮሐንስ በእግዚአብሄር የተላከ የሰው ዘር ወኪልና ሊቀ ካህኑ ከኢየሱስ 6 ወር በፊት ቀድሞ የተላከም መልዕክተኛ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ዮሐንስ የዓለምን ሐጢያቶች ወደ ኢየሱስ ያስተላለፈ የመጨረሻው ሊቀ ካህን ነበር፡፡ አጥማቂው ዮሐንስ የእግዚአብሄር ባርያ ነበር፡፡