Search

Często Zadawane Pytania na temat Wiary Chrześcijańskiej

Temat 1: Ponowne narodziny z wody i Ducha

1-8. ሐጢያቶቻችንን መናዘዝ እንዲጠፉ ሊያደርጋቸው ይችላልን? 

አይችልም፡፡ ሐጢያቶች በኑዛዜ አይወገዱም፡፡ የሚወገዱት በውሃውና በመንፈሱ ወንጌል እምነት ነው፡፡ ከሐጢያቶቻችን ባነጻን በኢየሱስ ጥምቀትና ደም ስናምን ብቻ ነው፡፡ በዮርዳኖስ በጥምቀቱ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ያነጻው የኢየሱስ መንፈሳዊ ደህንነት ወንጌል ይህ ነው፡፡  
የሐጢያቶች ኑዛዜ አንድ ሰው የእግዚአብሄርን ሕግ የሚያውቅበት ብቸኛው መረጃ ነው፡፡ ነገር ግን ቤዛነት ሊሰጠን የሚችለው በኢየሱስ ጥምቀትና መስቀል ስናምን ብቻ ነው፡፡
እርሱ የተጠመቀበት ውሃና የኢየሱስ ደም ሰዎችን ሁሉ ከሐጢያት ያዳነ የሰማይ እውነት ነው፡፡ ደህንነታችን የተመሰረተው ኢየሱስ የሰዎችን ሁሉ ሐጢያት እንደወሰደ በማመን ላይ እንጂ በሐጢያቶች ኑዛዜ ላይ አይደለም፡፡ የኢየሱስ ስቅለት ከእኛ ከሐጢያተኞች ለወሰዳቸው ለእነዚያ ሐጢያቶች በሙሉ የተቀበለው ቅጣት ነው፡፡  
ስለዚህ እውነተኛው ደህንነታችን ያለው በዮርዳኖስ በሆነው ጥምቀትና በመስቀል ላይ በፈሰሰው ደም ላይ ነው፡፡ እኛ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ የነጻነው ሐጢያቶቻችንን በሙሉ ባነጻው በኢየሱስ በማመናችን ነው፡፡     
ሐጢያቶቻችንን በመናዘዝ መዳን እንደምንችል የሚሰብኩ ሰዎች የእግዚአብሄርን ደህንነት የማያውቁ ሰዎች ናቸው፡፡ 
ስለዚህ የእግዚአብሄር ደህንነት በሆነው የኢየሱስ ጥምቀትና ደም ማመን አለብን፡፡ መቼም ቢሆን የሰው ዘር ሐጢያቶች እነርሱን ለእግዚአብሄር በመናዘዝ ይቅር ሊባሉ ይችላሉ አትበሉ፡፡ 
ሐጢያቶቻችን ሲዖል እንዳስቀመጡን እወቁ፡፡ ነገር ግን ባዳነንና በእግዚአብሄር ፊት ጻድቃን ባደረገን በኢየሱስ በጥምቀቱና በደሙ ማመናችን ሐጢያቶቻችንን ማስወገድ ይችላል፡፡ ከሐጢያቶቻችን ሁሉ መዳን የምንችልበት ብቸኛው መንገድ ይህ ነው፡፡ ሁላችንም በአንድ ጊዜ ከሐጢያቶቻችን የነጻነው የውሃውንና የደሙን የእውነት ቃሎች በማመናችን መሆኑን እንወቅ፡፡ (1ኛ ዮሐንስ 5፡4-8)   
በተናዘዝን ጊዜ ሁሉ ሐጢያቶቻችንን አይደመስሱም፡፡ በኑዛዜ ላይ በመደገፍ ሙጭጭ የምትሉ ከሆነ መጨረሻችሁ ሲዖል ይሆናል፡፡ በልባችን ውስጥ ያሉት ሐጢያቶች ይነጹ ዘንድ በእውነተኛው ወንጌል እንመን፡፡ በጭንቅላታችሁ ብቻ ሳይሆን በልባችሁም እመኑ፡፡ ለዘላለምም ከሐጢያቶቻችሁ ነጻ ሁኑ፡፡