1-32. በአንተ አባባል መሰረት ኢየሱስ ያለፉትን አሁን ያሉትንና ወደፊት ሐጢያቶችን በሙሉ ቀድሞውኑም አስወግዶዋል ካልን በኢየሱስ ጥምቀትና መስቀል በማመን ቀድሞውኑም ሐጢያቶቹ ይቅር የተባሉ የመሆኑን እውነታ በማሰብ ያለ ማቋረጥ ሐጢያትን ቢሰራ የግለሰቡ ዕጣ ፈንታ እንዴት ይሆናል? ይህ ሰው ሌላ ሰው ቢገድል እንኳን በኢየሱስ አማካይነት በመስቀል ላይ ለዚህ አይነቱ ሐጢያትም እንኳን ይቅርታን እንዳገኘ ያውቃል፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ ወደፊት የሚሰራቸውን እነዚህን ሐጢያቶች ቀድሞውኑም እንዳስወገደለት በማመን ያለ ምንም ማመንታት ሐጢያት በመስራት ይቀጥላል፡፡ እባክህ እነዚህን ነገሮች አብራራልኝ፡፡