Search

পুস্তক সমলোচনা

በውኑ ከውሃና ከመንፈስ ዳግመኛ ተወልዳችኋልን?

  • Yonas Kuliso
  • Ethiopia
  • 1812
  • 02/27/2024

Amharic 1

በውኑ በውሃውና በመንፈሱ ዳግም ተወልዳችኋልን? [አዲስ የተከለሰ ዕትም]

Rev. Paul C. Jong

  • ISBN9788928262168
  • পৃষ্টা348
  • রেটিং

በነገር ሁሉ መረዳትን የሰጠኝ እግዚአብሔር የተመሰገ ይሁን። እኔ ይህንን መጽሐፍ በአንድ አጋጣሚ ነው የተገናኘሁት። በonline ላይ ብዙ ጊዜዬን አጠፋ ነበረ። በአንድ አጋጣሚ አንድ መልዕክት በfacebook ስመላለስ አየሁ። ምንም ያህል በሳሙና ብትታጠብም ከሰልን ነጭ ማድረግ እንደማይቻልና በየቀኑ በምናቀርበው የንሰሐ ጸሎት ከሐጢአት እስራት ነጻ መውጣት እንደማንችል ጽሑፉ ያወሳ ነበር።

እኔም ተገረምኩና ጽሑፎቹን ማንበብ ጀመርኩ። እጅግም እንግዳ ነገር እንደሆነ አስቤ ነጻ የምታደል መጽሐፍ የምለውን አይቼ ለራሴም እንድደርሰኝ መልዕክት አስቀመጥኩ። መጽሐፉም በደረሰኝ ጊዜ ማንበብን ጀመርኩ። ገና እንደጀመርኩ ውስጤ በጥያቄዎች ተሞልቶ ነበረ።

መጽሐፉን እስካነበብኩበት ቀን ድረስ እውነተኛ የሰው ልጅ ማንነት ምን እንደሆነ፣ ሐጢአት በትክክል ምን እንደሆነ፣ እግዚአብሔር ሕግን ለምን እንደሰጠ፣ በብሉይ ኪዳን የነገረው የእጆች መጫን ምን ማለት እንደሆነ፣ ኢየሱስ በዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ለምን እንደተጠመቀ፣ እናም የአለም ሐጢአት ስባል ምን እንደነበረ፣ ኢየሱስ የትኛውን ሐጢአት እንዳስወገደና አሁን ያልተወገደ ሐጢአት አለ ወይ? ለምሉና ሌሎችም ጥያቄዎች ምላሽ ከመጽሐፉ ሳገኝ ገና ሳቅ ይቀድመኝ ጀመረ።

በፕሮቴስታንት ቤተ እምነት ውስጥ በነበርኩበት ጊዜ አንድም ቀን ስለ ኢየሱስ ጥምቀትና ስለ እጆች መጫን ሰምቼ አላውቅም። በዚህ መጽሐፍ ግን እግዚአብሔር አይኖቼን ሙሉ በሙሉ ገለጣቸው።

አሁን በውሃውና በመንፈስ ወንጌል በማመን የሐጢአት ስርየትን አግንቻለሁ። በኢየሱስ ጥምቀትና ሞት ሙሉ በሙሉ ሐጢአት አልባ ሆኛለሁ። እግዚአብሔር እንደ እኔ አይነቱን ደካማ ሰው ለማዳን መጣ። በጥምቀቱም ሐጢአቶቼን በሙሉ በስጋ ተሸከመ። ለእነዚያ ሐጢአቶችም በመስቀል ላይ ተቸነከረ። በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተነስቶ አዲስ ሕይወት ሰጠኝ። እግዚአብሔር ይመስገን አሁን ኑሮዬ በእምነት ነው። በማየት አልመላለስም። ክብር ሁሉ ለውሃና ለመንፈሱ ወንጌል ይሁን