Search

שאלות נפוצות על האמונה הנוצרית

נושא 4: שאלות נפוצות מקוראי ספרינו

4-12. የዘመኑን የክርስቲያን ተዓምራቶች የምታስባቸው እንዴት ነው? የመንፈስ ቅዱስ ሥራዎች አይደሉምን? መንፈስ ቅዱስ አሁንም በእግዚአብሄር ቤተክርስቲያን ውስጥ እንደሚሠራ አስባለሁ፡፡

በዛሬዎቹ የክርስቲያን ተዓምራቶች ጉዳይ ላይ በጠየከው ጥያቄ በከፊል ትክል ነህ፡፡ 
ነገር ግን መለኮታዊ ተዓምራቶች በሙሉ ለሰዎች በኢየሱስ ክርስቶስ የማመን እምነት ሊሰጡዋቸው እንደሚገባ ማስታወስ ይኖርብሃል፡፡ (ዮሐንስ 2፡11) በሌላ አነጋገር ጌታ ተዓምራቶችን የሚፈቅደው ሰዎች በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ እምነት እንዲኖራቸው ለመፍቀድ ነው፡፡
በሐዋርያትና በደቀ መዛሙርት በተለይም በሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ውስጥ የተፈጸሙ ብዙ ተዓምራቶችን ማግኘት እንችላለን፡፡ እነርሱ በተዓምራቶቹ አማካይነት ኢየሱስ አምላክ ለመሆኑ፣ ሐጢያቶቻችንን በሙሉ በጥምቀቱ ለመውሰዱና በመስቀል ላይ ደሙን በማፍሰስም ለሐጢያቶቻችን በሙሉ ካሳ ለመክፈል ለመሞቱ እውነት ያላቸውን እምነት መሰከሩ፡፡  
ነገር ግን የተጻፈው የእግዚአብሄር ቃል ከተጠናቀቀ በኋላ እግዚአብሄር አብ ተዓምራዊ ማስረጃዎችን ከመሻት ይልቅ የእርሱን ቃል እንድንታዘዝ ይፈልግብናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ የሚለው ለዚህ ነው፡- ‹‹ፍቅር ለዘላለም አይወድቅም፤ ትንቢት ቢሆን ግን ይሻራል፤ ልሳኖች ቢሆኑ ይቀራሉ፤ እውቀትም ቢሆን ይሻራል፡፡ ከእወቀት ከፍለን እናውቃለንና፤ ከትንቢትም ከፍለን እንናገራለንና፤ ፍጹም የሆነ ሲመጣ ግን ተከፍሎ የነበረው ይሻራል፡፡›› (1ኛ ቆሮንቶስ 13፡8-10) 
  
እውነተኛ እምነት ቀድሞውኑም ከጌታ በተቀበልከው የእግዚአብሄር ቃል ላይ እንጂ በተለማመድካቸው ተዓምራቶች ላይ የተመሠረተ አይደለም፡፡
ወደ ዝርዝሩ ተመለስ